- July 16, 2026, 6:50 p.m.
- 14
የሰ/ት/ቤቱ የ3 ዓመት የአገልግሎት ሪፖርት በጠቅላላ ጉባኤው ጸደቀ። የደ/ነ/ቅ/ዮሐንስ እና መ/ጎ/ቅ/ማርያም ቤ/ክ የፍቁረ እግዚእ ሰ/ት/ቤት በ2016 የተመረጠው ሥራ አመራር 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ያለፉትን 3 ዓመት የአገልግሎት ሪፖርት የሰ/ት/ቤቱ አባላት በተገኙበት በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርቧል ። በጠቅላላ ጉባኤው ላይ በሰንበት ት/ቤቱ ባለፉት 3 ዓመት የተከናወኑ አገልግሎቶችን በተመለከተ ሪፖርት በሰንበት ት/ቤቱ ሰብሳቢ ዳግም ጌታቸው ቀርቧል። በአገልግሎት ሪፖርት ዙሪያ…
- July 15, 2026, 12:30 p.m.
- 17
የእርስዎ ሃሳብ ለሰንበት ት/ቤታችን እድገት ወሳኝነት አለው 🔔🔔🔔ጠቅላላ ጉባኤ🔔🔔🔔 📆 ሐሙስ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም 🕰 ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ⛪️ በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በጠቅላላ ጉባኤው ላይ በመገኘት የአባልነት ግዴታዎን ይወጡ‼
- July 14, 2026, 12:30 p.m.
- 17
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የሚኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሮዝማውንት ሚኒሶታ የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ወቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ባጋጠመው የእሳት አደጋ የተሰማቸውን ኃዘን ገለጹ። በሚኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከታችን ውስጥ ከሚገኙት አብያተ ክርስቲያናት መካከል በROSEMOUNT, MINNESOTA በቅርብ ጊዜ ከ2.2 ሚሊዮን ዶላር በላይ የተገዛው እና በቅርቡ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ወቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ዛሬ ሐምሌ ፮ (Jul, 13) የሰማዕቷ ቅድ…
- July 13, 2026, 1:20 p.m.
- 18
በመቀጠልም በዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው አጠቃላይ የሥልጠናውን ይዘትና አካሄድ ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሥልጠናው በ3 መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን እነርሱም መሠረተ እምነት ዶግማ እና የሥርዓተ አምልኮ ጉዳዮች ፣ ሥርዓተ ትምህርትን የሚመለከቱ ሥልጠናዎች እንዲሁም ተግባራዊ ሥራና የሕይወት ክህሎት ናቸው። በሥልጠናውም ላይ ከ37 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ ከ315 በላይ ሠልጣኞች ይሳተፋሉ። ©የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
- July 13, 2026, 1:20 p.m.
- 20
በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተጀመረ። ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ አገልግሎት መምርያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ፣ ሊቀ ጉባኤ መሐሪ የ…