በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን.
የአዲስ አበባ ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ከተማ በድሮ አጠራር ከፍተኛ 1 ቀበሌ 03 የሚገኝ ሲሆን አሁን በአራዳ ክፍለ ከተማ ከፒያሳ መናገሻ ገነተ ጽጌ (አራዳ) ቅዱስ ጊዮርጊስ ተነሥቶ በሰሜናዊ ምዕራብ አቅጣጫ ወደ አስኮ በተዘረጋው የአርበኞች መንገድ በራስ ደስታ ሆስፒታል አካባቢ ይገኛል::
ከመንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የ3.6 ኪ ሜ ርቀት ያለው ሲሆን ስሙ ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ መባሉ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ( የነጎድጓድ ልጅ ) ተብሎ ስለሚጠራ ነው ፡፡
ስለ እኛ የበለጠየደብሩ አገልግሎት
የደብሩ አገልግሎት ለምእመናን መንፈሳዊ፣ ማህበራዊና አስተዳደራዊ ፍላጎቶች ሁሉ የሚመለስ ሰፊ አገልግሎት ይሰጣል። ከአዲስ የሰበካ ጉባኤ አባልነት ምዝገባና ክፍያ ጀምሮ፣ የክርስትና አገልግሎቶች፣ ፍትሐት፣ ጸሎትና ቅዳሴ፣ የቀብር ሥርዓት፣ የሥርዓተ ጋብቻ ሙሉ አገልግሎት፣ እንዲሁም የአዳራሽ ኪራይ እና ልዩ ልዩ መደጋገፊያ አገልግሎቶች በቅዱስ ሥርዓትና በተገቢ አስተዳደር ይፈጸማሉ። እነዚህ አገልግሎቶች ሁሉ የምእመናንን መንፈሳዊ ሕይወት ለማጠናከር እና የማህበረሰቡን አንድነት ለማጎልበት የታሰቡ ናቸው።
የደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን አለቃዎች.
የደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን አለቃዎች በእምነት፣ በትምህርትና በመንፈሳዊ አገልግሎት የተለዩ አባቶችና መምህራን ሲሆኑ፣ ቤተ ክርስቲያኑን በቅዱስ ሥርዓትና በጥበብ በመመራት ለምእመናን መንፈሳዊ መመሪያና አገልግሎት ይሰጣሉ። እስከ ዛሬ ድረስ በዚህ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተለያዩ ዘመናት አገልግሎት ያደረጉ አለቃዎች ቁጥራቸው 24 ደርሶአል፤ እነርሱም በዜማ፣ በትምህርት፣ በካህናት አስተዳደርና በመንፈሳዊ ሕይወት ሁሉ ትልቅ አሻራ ተውተዋል።
ቤተሳይዳ (ጠበል ቤት)
የጠበል ቤቱ ቦታ የሚገኘው ከቤተ ክርስቲያኑ በስተደቡብ አቅጣጫ ሲኾን የሚሸፍነው የቅዳ ስፋት 2,100 m2 ነው፡፡ የጠበል ቤቱ ምንም እንኳን የዮሐንስ ጠበል ተብሎ በዋነኛነት ቢጠራም ነገር ግን በጠበል ቤቱ ግቢ ውስጥ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡.
ፍኖተ ብርሃን
ባሕረ ጥበባት መጽሔት
ሁሉንም ይመልከቱሰሌዳ መጽሔት
ሁሉንም ይመልከቱአግናጥዮስ (ለህፃናት) መጽሔት
ሁሉንም ይመልከቱዝክረ ቅዱሳን
እግዚአብሔር ዛሬ ያልቃል: ነገ ይደቃል የማይባለውን የድንግል እናቱን ፍቅር አብዝቶ ያድለን:: በረከቷም በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር::አሜን
እግዚአብሔር ዛሬ ያልቃል: ነገ ይደቃል የማይባለውን የድንግል እናቱን ፍቅር አብዝቶ ያድለን:: በረከቷም በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር::አሜን 😘7❤3🥰2😍2