September 07, 2026
ዜና (News)
7
የዓመቱን የመጨረሻ የደም ልገሳ መርሐ ግብር ተካሄደ።
የዓመቱን የመጨረሻ የደም ልገሳ መርሐ ግብር ተካሄደ።
በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎለጎታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የፍቁረ እግዚእ ሰ/ት/ቤት ከኢትዮጵያ ደምና ሕብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት ጋር በመተባበር የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ።
በተዘጋጀው የደም መለገስ መርሐ ግብር ላይ የደብሩ አገልጋዮች ፣ የሰንበት ት/ቤቱ አባላት እና ምዕመናንን በአጠቃላይ ከ182 በላይ ሰዎች ደማቸውን እንዲለግሱ የተደረገ ሲሆን በዚህም ከ546 በለይ በደም እጦት በሞትና በህይወት መካከል ለሚገኙ ወገኖችን የተለገሰው ደም ሕይወት ማትረፍ እንደሚያስችል የጤና ባለሙያዎች ገልጸዋል ።
የደብሩ ማሕበረ ካህናት ፣ የሰንበት ት/ቤቱ አባላት እና ምእመናን በተለያየ ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች ደም በመለገስ ሕይወታቸውን ከሞት ለመታደግ ለምታደርጉት አስተዋጾ ሰ/ት/ቤቱ ምስጋና ያቀርባል።
ደም በመለገስ የወገኖቻችን ሕይወት እንታደግ‼